Tuesday, 23 August 2022

አፄ ዘርዓ ያዕቆብ በመልክአ ማርያም ድርሰታቸው

 



አፄ ዘርዓ ያዕቆብ በመልክአ ማርያም ድርሰታቸው እንዲህ ሲሉ ለእመቤታችን ምስጋናን አቀረቡ።  

 

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ መካነ ፍሥሓ ምጡቀ፡ በአእባነ ባሕርይ ዘተነድቀ፡ 

ማርያም ድብተራ እንተ ኢትትከደኒ ሠቀ፡ 

ጽሒፈ ውዳሴኪ እምኪ ኀልቀ ሶበ ኮነ ጥቀ፡ ዝናመ ክረምት ቀለመ ወሰማይ ረቀ።


እመቤቴ ማርያም ሆይ ምጡቅና ሩቅ ወደሚሆን የደስታ ቦታ ላረገ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል። ይኸውም ኅብሩ ሊመረምሩት በማይቻል ዕንቁ የታነፀ ሕንፃ ይገኝበታል። ድንግል ሆይ የማቅና የጨርቅ ያይደለ የብርሃን ድንኳን ነሽ። የክረምት ዝናም ቀለም ሰማያት ወረቀት ቢሆኑ ምስጋናህ ተጽፎ የሚያልቅ አይደለም። 


ስብሐት ለኪ ማርያም በኁልቆ ኩሉ ሥዕርትየ

ስብሐት ለኪ ማርያም በኁልቆ ኩሉ አዕፅምትየ 

ስብሐት ለኪ ማርያም በኁልቆ ኩሉ ዘተርእየ

ስብሐት ለኪ ንግሥትየ በኁልቆ ኩሉ ዘኢያስተርእየ 

ስብሐተ ድንግልናኪ ዘልፈ ይነግር አፉየ


እመቤቴ ማርያም ሆይ በራስ ፀጉሬ ቁጥር አመሰግንሻለሁ። በአጥንቶቼ ቁጥር አመሰግንሻለሁ። ድንግል ሆይ በሚታየውና በሚዳሰሰው ሁሉ ቁጥር አመሰግንሻለሁ። 

ንግሥት ሆይ በማይታየውና በማይዳሰሰው ሁሉ ቁጥር ሰላም እያልሁ የድንግልናሽን ምስጋና አፌ ሁል ጊዜ ይናገራል።


ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ያካፍለን። 

የአባቶቻችንን መንፈስ ያሳድርብን።

No comments:

Post a Comment

አፄ ዘርዓ ያዕቆብ በመልክአ ማርያም ድርሰታቸው

  አፄ ዘርዓ ያዕቆብ በመልክአ ማርያም ድርሰታቸው እንዲህ ሲሉ ለእመቤታችን ምስጋናን አቀረቡ።     ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ መካነ ፍሥሓ ምጡቀ፡ በአእባነ ባሕርይ ዘተነድቀ፡  ማርያም ድብተራ እንተ ኢትትከደኒ ሠቀ፡  ጽሒፈ ...